የኒጄር ወታደራዊና ፀጥታ ኃይላት የአገሪቱን ፕሬዚደንት ከስልጣን ያወረዱ መሆኑን አስታወቁ

ዩናይትድ ስቴትስና ኔዘርላንድስ 1 ለ 1 ተለያዩ

Niger.jpg

ORTN - Télé Sahel on July 26, 2023, shows Colonel Major Amadou Abdramane (C), spokesperson for the National Committee for the Salvation of the People (CNSP), speaking during a televised statement. Credit: ORTN - Télé Sahel/AFP via Getty Images

ከትናንት ረቡዕ ማለዳ አንስቶ የኒጄር ፕሬዚደንት መሐመድ ባዙምን በእገታ በቁጥጥራቸው ስር አውለው የነበሩት ወታደሮች ፕሬዚደንቱን ከስልጣን ማውረዳቸውን፣ ሕገ መንግሥቱን ማገዳቸውን፣ ማናቸውንም ተቋማትና የአገሪቱ የአየርና የየብስ ድንበሮችን የዘጉ መሆኑን በቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።

የመፈንቅለ መንግሥት አካሂያጆቹ መሪ ኮሎኔል ሜጀር አማዱ አብድራማን የመከላከያና የፀጥታ ኃይላቱ እርምጃውን በጋራ እንደወሰዱ ገልጠዋል።

የአገዛዝ ለውጥ ለማካሔድ የተነሳሱትም "የፀጥታ ሁኔታ ማሽቆልቆ፣ የምጣኔ ኃብትና ማሕበራዊ አስተዳደር ብቃት ማነስን" ለመግታት እንደሆነ ተናግረዋል።

ፕሬዚደንት ባዝሙም የዩናይትድ ስቴትስ ብርቱ አጋር የነበሩ ሲሆን፤ የወታደራዊና ፀጥታ ኃይላቱን የቴሌቪዥን መግለጫ ተከትሎ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ፕሬዚደንቱ እንዲለቀቁ ጥሪ አቅርበዋል።

የዓለም ዋንጫ

ዩናይትድ ስቴትስና ኔዘርላንድስ ዛሬ ረፋዱ ላይ በዌሊንግተን ሪጂናል ስታዲየም ባደረጉት የሴቶች ዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ግጥሚያ1 ለ 1 ተለያይተዋል።
US V Netherlands.jpg
Naomi Girma of USA (L) fights for the ball with Katja Snoeijs of Netherlands (R) during the FIFA Women's World Cup Australia & New Zealand 2023 Group E match between USA and Netherlands at Wellington Regional Stadium on July 27, 2023, in Wellington, New Zealand. Credit: Daniela Porcelli/Eurasia Sport Images/Getty Images
ኔዘርላንድስ በመጀመሪያው ግማሽ ጨዋታ በጂል ሩርድ አማካይነት በ17ኛዋ ደቂቃ የመሪነት ግብ ብታስቆጥርም፤ ዩናይትድ ስቴትስ በሊንድዚ ሆራን በኩል በ62ኛዋ ደቂቃ ባገባችው ግብ አቻ ለአቻ ለመለያየት በቅተዋል።


Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service